- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									11
									 
									 
									|2 Corintios 12:11|
									በመመካቴ ሞኝ ሆኜአለሁ፤ እናንተ ግድ አላችሁኝ፤ እናንተ እኔን ልታመሰግኑ ይገባ ነበርና። እኔ ምንም ባልሆን እንኳ፥ ከዋነኞቹ ሐዋርያት በምንም አልጎድልምና።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|2 Corintios 12:12|
									በእርግጥ የሐዋርያነት ምልክት በመካከላችሁ በምልክትና በድንቅ ነገር በተአምራትም በሁሉ ትዕግሥት ተደረገ።									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|2 Corintios 12:13|
									እኔ ራሴ ካልከበድሁባችሁ ከዚህ በቀር፥ ከሌላ ቤተ ክርስቲያን ያነሳችሁበት በምን እኮ ነው? ይህን በደሌን ይቅር በሉልኝ።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|2 Corintios 12:14|
									እነሆ፥ ወደ እናንተ እመጣ ዘንድ ስዘጋጅ ይህ ሦስተኛዬ ነው፤ አልከብድባችሁምም፥ እናንተን እንጂ ያላችሁን አልፈልግምና። ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ ሊያከማቹ አይገባቸውምና።									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|2 Corintios 12:15|
									እኔ ግን ስለ ነፍሳችሁ በብዙ ደስታ ገንዘቤን እከፍላለሁ፥ ራሴን እንኳ እከፍላለሁ። ከመጠን ይልቅ ብወዳችሁ በዚህ ልክ ፍቅራችሁ የሚያንስ ነውን?									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|2 Corintios 12:16|
									ይሁን እንጂ እኔ አልከበድሁባችሁም፤ ነገር ግን ሸንጋይ ሆኜ በተንኰል ያዝኋችሁ።									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|2 Corintios 12:17|
									ወደ እናንተ ከላክኋቸው በአንዱ ስንኳ አታለልኋችሁን?									
									    
								 
- 
									
									18
									 
									 
									|2 Corintios 12:18|
									ቲቶን መከርሁት ከእርሱም ጋር ወንድሙን ላክሁት፤ ቲቶስ አታለላችሁን? በአንድ መንፈስ አልተመላለስንምን? በአንድ ፍለጋስ አልተመላለስንም?									
									    
								 
- 
									
									19
									 
									 
									|2 Corintios 12:19|
									ለእናንተ ስለ ራሳችን እንድንመልስ ሁልጊዜ ይመስላችኋልን? በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን፤ ነገር ግን፥ ወዳጆች፥ እናንተን ልናንጻችሁ ሁሉን እንናገራለን።									
									    
								 
- 
									
									20
									 
									 
									|2 Corintios 12:20|
									ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18