- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									11
									 
									 
									|2 Corintios 2:11|
									በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|2 Corintios 2:12|
									ስለ ክርስቶስም ወንጌል ወደ ጢሮአዳ በመጣሁ ጊዜ፥ ለጌታ ሥራ በር ምንም ቢከፈትልኝ፥ ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ ዕረፍት አልነበረውም፥									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|2 Corintios 2:13|
									ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|2 Corintios 2:14|
									ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|2 Corintios 2:15|
									በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|2 Corintios 2:16|
									ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|2 Corintios 2:17|
									የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 14-15