- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									11
									 
									 
									|2 Corintios 4:11|
									የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ እኛ ሕያዋን የሆንን ከኢየሱስ የተነሣ ዘወትር ለሞት አልፈን እንሰጣለንና።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|2 Corintios 4:12|
									ስለዚህ ሞቱ በእኛ ሕይወቱም በእናንተ ይሠራል።									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|2 Corintios 4:13|
									ነገር ግን። አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|2 Corintios 4:14|
									ጌታን ኢየሱስን ያስነሣው እኛን ደግሞ ከኢየሱስ ጋር እንዲያስነሣን ከእናንተም ጋር እንዲያቀርበን እናውቃለንና።									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|2 Corintios 4:15|
									በብዙዎች በኩል የተትረፈረፈው ጸጋ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋናን ያበዛ ዘንድ፥ ሁሉ ስለ እናንተ ነውና።									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|2 Corintios 4:16|
									ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል።									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|2 Corintios 4:17|
									የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18