- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									11
									 
									 
									|2 Corintios 6:11|
									እናንተ የቆሮንቶስ ሰዎች ሆይ፥ አፋችን ለእናንተ ተከፍቶአል ልባችንም ሰፍቶላችኋል፤									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|2 Corintios 6:12|
									በእኛ አልጠበባችሁም በሆዳችሁ ግን ጠቦባችኋል፤									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|2 Corintios 6:13|
									ልጆቼ እንደ መሆናችሁ ግን እላችኋለሁ፥ እናንተ ደግሞ ብድራት መልሳችሁልን ተስፋፉ።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|2 Corintios 6:14|
									ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|2 Corintios 6:15|
									ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|2 Corintios 6:16|
									ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው? እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነንና እንዲሁም እግዚአብሔር ተናገረ እንዲህ ሲል። በእነርሱ እኖራለሁ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸውም እሆናለሁ እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|2 Corintios 6:17|
									ስለዚህም ጌታ። ከመካከላቸው ውጡና የተለያችሁ ሁኑ ርኵስንም አትንኩ ይላል፤ ሁሉንም የሚገዛ ጌታ። እኔም እቀበላችኋለሁ፥ ለእናንተም አባት እሆናለሁ እናንተም ለእኔ ወንድ ልጆችና ሴት ልጆች ትሆናላችሁ ይላል።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18