-
-
Amharic (NT)
-
-
22
|Apocalipsis 21:22|
ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክና በጉ መቅደስዋ ናቸውና መቅደስ በእርስዋ ዘንድ አላየሁም።
-
23
|Apocalipsis 21:23|
ለከተማይቱም የእግዚአብሔር ክብር ስለሚያበራላት መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ፥ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጓትም ነበር።
-
24
|Apocalipsis 21:24|
አሕዛብም በብርሃንዋ ይመላለሳሉ፥ የምድርም ነገሥታት ክብራቸውን ወደ እርስዋ ያመጣሉ፤
-
25
|Apocalipsis 21:25|
በዚያም ሌሊት ስለሌለ ደጆችዋ በቀን ከቶ አይዘጉም፥
-
26
|Apocalipsis 21:26|
የአሕዛብንም ግርማና ክብር ወደ እርስዋ ያመጣሉ።
-
27
|Apocalipsis 21:27|
ለበጉም በሆነው በሕይወት መጽሐፍ ከተጻፉት በቀር፥ ጸያፍ ነገር ሁሉ ርኵሰትና ውሸትም የሚያደርግ ወደ እርስዋ ከቶ አይገባም።
-
-
Sugerencias
Haga clic para leer 2 Reyes 6-8