-
Leer por capítulos:
-
Amharic (NT)
-
-
11
|Mateo 24:11|
ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤
-
12
|Mateo 24:12|
ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።
-
13
|Mateo 24:13|
እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
-
14
|Mateo 24:14|
ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።
-
15
|Mateo 24:15|
እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥
-
16
|Mateo 24:16|
በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉት ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥
-
17
|Mateo 24:17|
በሰገነትም ያለ በቤቱ ያለውን ሊወስድ አይውረድ፥
-
18
|Mateo 24:18|
በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ።
-
19
|Mateo 24:19|
በዚያችም ወራት ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው።
-
20
|Mateo 24:20|
ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤
-
-
Sugerencias
Haga clic para leer Levítico 8-10