- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									11
									 
									 
									|2 Corintios 11:11|
									ስለ ምን? ስለማልወዳችሁ ነውን? እግዚአብሔር ያውቃል።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|2 Corintios 11:12|
									ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ ምክንያትን ከሚፈልጉቱ ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|2 Corintios 11:13|
									እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|2 Corintios 11:14|
									ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|2 Corintios 11:15|
									እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|2 Corintios 11:16|
									እንደ ገና እላለሁ። ለማንም ሰው ሞኝ የሆንሁ አይምሰለው፤ ያለዚያ ግን እኔ ደግሞ ጥቂት እመካ ዘንድ እንደ ሞኝ እንኳ ሆኜ ተቀበሉኝ።									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|2 Corintios 11:17|
									እንደዚህ ታምኜ ስመካ የምናገረው፥ በሞኝነት እንጂ ጌታ እንዳዘዘኝ አልናገርም።									
									    
								 
- 
									
									18
									 
									 
									|2 Corintios 11:18|
									ብዙዎች በዓለማዊ ነገር ስለሚመኩ እኔ ደግሞ እመካለሁ።									
									    
								 
- 
									
									19
									 
									 
									|2 Corintios 11:19|
									ልባሞች ስለምትሆኑ በደስታ ሞኞችን ትታገሣላችሁና፤									
									    
								 
- 
									
									20
									 
									 
									|2 Corintios 11:20|
									ማንም ባሪያዎች ቢያደርጋችሁ፥ ማንም ቢበላችሁ፥ ማንም ቢቀማችሁ፥ ማንም ቢኮራባችሁ፥ ማንም ፊታችሁን በጥፊ ቢመታችሁ ትታገሣላችሁና።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18