-
-
Amharic (NT)
-
-
41
|Juan 6:41|
እንግዲህ አይሁድ። ከሰማይ የወረደ እንጀራ እኔ ነኝ ስላለ ስለ እርሱ አንጐራጐሩና።
-
42
|Juan 6:42|
አባቱንና እናቱን የምናውቃቸው ይህ የዮሴፍ ልጅ ኢየሱስ አይደለምን? እንግዲህ። ከሰማይ ወርጃለሁ እንዴት ይላል? አሉ።
-
43
|Juan 6:43|
ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እርስ በርሳችሁ አታንጐራጕሩ።
-
44
|Juan 6:44|
የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
-
45
|Juan 6:45|
ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል።
-
46
|Juan 6:46|
አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል።
-
47
|Juan 6:47|
እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።
-
48
|Juan 6:48|
የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
-
49
|Juan 6:49|
አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤
-
50
|Juan 6:50|
ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው።
-
-
Sugerencias
Haga clic para leer Levítico 11-12