-
-
Amharic (NT)
-
-
56
|Lucas 1:56|
ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች።
-
57
|Lucas 1:57|
የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች።
-
58
|Lucas 1:58|
ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው።
-
59
|Lucas 1:59|
በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ።
-
60
|Lucas 1:60|
እናቱ ግን መልሳ። አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ አለች።
-
61
|Lucas 1:61|
እነርሱም። ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም አሉአት።
-
62
|Lucas 1:62|
አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት።
-
63
|Lucas 1:63|
ብራናም ለምኖ። ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ።
-
64
|Lucas 1:64|
ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ።
-
65
|Lucas 1:65|
ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤
-
-
Sugerencias
Haga clic para leer Levítico 8-10