- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									14
									 
									 
									|Santiago 1:14|
									ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል።									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|Santiago 1:15|
									ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|Santiago 1:16|
									የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ አትሳቱ።									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|Santiago 1:17|
									በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ።									
									    
								 
- 
									
									18
									 
									 
									|Santiago 1:18|
									ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን።									
									    
								 
- 
									
									19
									 
									 
									|Santiago 1:19|
									ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤									
									    
								 
- 
									
									20
									 
									 
									|Santiago 1:20|
									የሰው ቍጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራምና።									
									    
								 
- 
									
									21
									 
									 
									|Santiago 1:21|
									ስለዚህ ርኵሰትን ሁሉ የክፋትንም ትርፍ አስወግዳችሁ፥ ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በየዋህነት ተቀበሉ።									
									    
								 
- 
									
									22
									 
									 
									|Santiago 1:22|
									ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።									
									    
								 
- 
									
									23
									 
									 
									|Santiago 1:23|
									ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18