- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									17
									 
									 
									|Santiago 2:17|
									እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።									
									    
								 
- 
									
									18
									 
									 
									|Santiago 2:18|
									ነገር ግን አንድ ሰው። አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።									
									    
								 
- 
									
									19
									 
									 
									|Santiago 2:19|
									እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።									
									    
								 
- 
									
									20
									 
									 
									|Santiago 2:20|
									አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?									
									    
								 
- 
									
									21
									 
									 
									|Santiago 2:21|
									አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?									
									    
								 
- 
									
									22
									 
									 
									|Santiago 2:22|
									እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?									
									    
								 
- 
									
									23
									 
									 
									|Santiago 2:23|
									መጽሐፍም። አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።									
									    
								 
- 
									
									24
									 
									 
									|Santiago 2:24|
									ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።									
									    
								 
- 
									
									25
									 
									 
									|Santiago 2:25|
									እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?									
									    
								 
- 
									
									26
									 
									 
									|Santiago 2:26|
									ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18