- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									7
									 
									 
									|Santiago 2:7|
									የተጠራችሁበትን መልካሙን ስም የሚሰድቡ እነርሱ አይደሉምን?									
									    
								 
- 
									
									8
									 
									 
									|Santiago 2:8|
									ነገር ግን መጽሐፍ። ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ እንደሚል የንጉሥን ሕግ ብትፈጽሙ መልካም ታደርጋላችሁ፤									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|Santiago 2:9|
									ለሰው ፊት ግን ብታደሉ ኃጢአትን ትሠራላችሁ፥ ሕግም እንደ ተላላፊዎች ይወቅሳችኋል።									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|Santiago 2:10|
									ሕግን ሁሉ የሚጠብቅ፥ ነገር ግን በአንዱ የሚሰናከል ማንም ቢኖር በሁሉ በደለኛ ይሆናል፤ አታመንዝር ያለው ደግሞ። አትግደል ብሎአልና፤									
									    
								 
- 
									
									11
									 
									 
									|Santiago 2:11|
									ባታመነዝርም፥ ነገር ግን ብትገድል፥ ሕግን ተላላፊ ሆነሃል።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|Santiago 2:12|
									በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች እንዲህ ተናገሩ፥ እንዲህም አድርጉ።									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|Santiago 2:13|
									ምሕረትን ለማያደርግ ምሕረት የሌለበት ፍርድ ይሆናልና፤ ምሕረትም በፍርድ ላይ ይመካል።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|Santiago 2:14|
									ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|Santiago 2:15|
									ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|Santiago 2:16|
									ከእናንተ አንዱም። በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18