- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									1
									 
									 
									|1 Corintios 13:1|
									በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ።									
									    
								 
- 
									
									2
									 
									 
									|1 Corintios 13:2|
									ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።									
									    
								 
- 
									
									3
									 
									 
									|1 Corintios 13:3|
									ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።									
									    
								 
- 
									
									4
									 
									 
									|1 Corintios 13:4|
									ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤									
									    
								 
- 
									
									5
									 
									 
									|1 Corintios 13:5|
									የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤									
									    
								 
- 
									
									6
									 
									 
									|1 Corintios 13:6|
									ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤									
									    
								 
- 
									
									7
									 
									 
									|1 Corintios 13:7|
									ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል።									
									    
								 
- 
									
									8
									 
									 
									|1 Corintios 13:8|
									ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል።									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|1 Corintios 13:9|
									ከእውቀት ከፍለን እናውቃለንና፥ ከትንቢትም ከፍለን እንናገራለንና፤									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|1 Corintios 13:10|
									ፍጹም የሆነ ሲመጣ ግን ተከፍሎ የነበረው ይሻራል።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18