- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									1
									 
									 
									|1 Corintios 15:1|
									ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤									
									    
								 
- 
									
									2
									 
									 
									|1 Corintios 15:2|
									በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፥ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ።									
									    
								 
- 
									
									3
									 
									 
									|1 Corintios 15:3|
									እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ። መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥									
									    
								 
- 
									
									4
									 
									 
									|1 Corintios 15:4|
									መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥									
									    
								 
- 
									
									5
									 
									 
									|1 Corintios 15:5|
									ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤									
									    
								 
- 
									
									6
									 
									 
									|1 Corintios 15:6|
									ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤									
									    
								 
- 
									
									7
									 
									 
									|1 Corintios 15:7|
									ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤									
									    
								 
- 
									
									8
									 
									 
									|1 Corintios 15:8|
									ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|1 Corintios 15:9|
									እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|1 Corintios 15:10|
									ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18