- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									1
									 
									 
									|1 Corintios 9:1|
									እኔ ነጻ አይደለሁምን? ሐዋርያስ አይደለሁምን? ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንስ አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ ሥራዬ አይደላችሁምን?									
									    
								 
- 
									
									2
									 
									 
									|1 Corintios 9:2|
									የሐዋርያነቴ ማኅተም በጌታ እናንተ ናችሁና ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን ለእናንተስ ምንም ቢሆን ሐዋርያ ነኝ።									
									    
								 
- 
									
									3
									 
									 
									|1 Corintios 9:3|
									ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን?									
									    
								 
- 
									
									5
									 
									 
									|1 Corintios 9:5|
									እንደ ሌሎቹ ሐዋርያትና እንደ ጌታ ወንድሞች እንደ ኬፋም፥ እኅት ሚስታችንን ይዘን ልንዞር መብት የለንምን?									
									    
								 
- 
									
									6
									 
									 
									|1 Corintios 9:6|
									ወይስ ሥራን ለመተው መብት የሌለን እኔና በርናባስ ብቻ ነን?									
									    
								 
- 
									
									7
									 
									 
									|1 Corintios 9:7|
									ከቶ በገዛ ገንዘቡ በወታደርነት የሚያገለግል ማን ነው? ወይስ ወይን ተክሎ ፍሬውን የማይበላ ማን ነው? ወይስ መንጋ እየጠበቀ ከመንጋው ወተት የማይጠጣ ማን ነው?									
									    
								 
- 
									
									8
									 
									 
									|1 Corintios 9:8|
									ይህን በሰው ሥልጣን ብቻ እላለሁን?									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|1 Corintios 9:9|
									ሕግስ ደግሞ ያን አይልምን? የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር ተብሎ በሙሴ ሕግ ተጽፎአልና። እግዚአብሔርስ ስለ በሬዎች ይገደዋልን?									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|1 Corintios 9:10|
									ይህን የሚለው ፈጽሞ ስለ እኛ አይደለምን? የሚያርስ በተስፋ ሊያርስ የሚያበራይም እንዲካፈል በተስፋ ሊያበራይ ስለሚገባው በእውነት ስለ እኛ ተጽፎአል።									
									    
								 
- 
									
									11
									 
									 
									|1 Corintios 9:11|
									እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን?									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 16-18