- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									6
									 
									 
									|1 Corintios 4:6|
									ወንድሞች ሆይ፥ ስለ አንዱ በአንዱ ላይ አንዳችሁም እንዳይታበዩ። ከተጻፈው አትለፍ የሚለውን በእኛ ትማሩ ዘንድ፥ ይህን በእናንተ ምክንያት ስለ ራሴና ስለ አጵሎስ እንደ ምሳሌ ተናገርሁ።									
									    
								 
- 
									
									7
									 
									 
									|1 Corintios 4:7|
									አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድር ነው?									
									    
								 
- 
									
									8
									 
									 
									|1 Corintios 4:8|
									አሁን ጠግባችኋል፤ አሁንስ ባለ ጠጎች ሆናችኋል፤ ያለ እኛ ነግሣችኋል፤ እኛ ደግሞ ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ብትነግሡ መልካም ይሆን ነበር።									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|1 Corintios 4:9|
									ለዓለም ለመላእክትም ለሰዎችም መጫወቻ ሆነናልና፤ እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች ከሁሉ ይልቅ የኋለኞች እንዳደረገን ይመስለኛልና።									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|1 Corintios 4:10|
									እኛ ስለ ክርስቶስ ሞኞች ነን እናንተ ግን በክርስቶስ ልባሞች ናችሁ፤ እኛ ደካሞች ነን እናንተ ግን ኃይለኞች ናችሁ፤ እናንተ የከበራችሁ ናችሁ እኛ ግን የተዋረድን ነን።									
									    
								 
- 
									
									11
									 
									 
									|1 Corintios 4:11|
									እስከዚህ ሰዓት ድረስ እንራባለን፥ እንጠማለን፥ እንራቆታለን፥ እንጐሰማለን፥ እንንከራተታለን፥									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|1 Corintios 4:12|
									በገዛ እጃችን እየሠራን እንደክማለን፤ ሲሰድቡን እንመርቃለን፥ ሲያሳድዱን እንታገሣለን፥ ክፉ ሲናገሩን እንማልዳለን፤									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|1 Corintios 4:13|
									እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጥራጊ የሁሉም ጉድፍ ሆነናል።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|1 Corintios 4:14|
									እንደምወዳችሁ ልጆቼ አድርጌ ልገሥጻችሁ እንጂ ላሳፍራችሁ ይህን አልጽፍም።									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|1 Corintios 4:15|
									በክርስቶስ አእላፍ ሞግዚቶች ቢኖሩአችሁ ብዙ አባቶች የሉአችሁም እኔ በክርስቶስ ኢየሱስ በወንጌል ወልጄአችኋለሁና።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 14-15