- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									8
									 
									 
									|1 Corintios 3:8|
									የሚተክልና የሚያጠጣ አንድ ናቸው፥ ነገር ግን እያንዳንዱ እንደ ራሱ ድካም መጠን የራሱን ደመወዝ ይቀበላል።									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|1 Corintios 3:9|
									የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንፃ ናችሁ፤ ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|1 Corintios 3:10|
									የእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ተሰጠኝ መጠን እንደ ብልሃተኛ የአናጺ አለቃ መሠረትን መሠረትሁ፥ ሌላውም በላዩ ያንጻል። እያንዳንዱ ግን በእርሱ ላይ እንዴት እንዲያንጽ ይጠንቀቅ።									
									    
								 
- 
									
									11
									 
									 
									|1 Corintios 3:11|
									ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|1 Corintios 3:12|
									ማንም ግን በዚህ መሠረት ላይ በወርቅ ቢሆን በብርም በከበረ ድንጋይም በእንጨትም በሣርም ወይም በአገዳ ቢያንጽ፥ የእያንዳንዱ ሥራ ይገለጣል፤									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|1 Corintios 3:13|
									በእሳት ስለሚገለጥ ያ ቀን ያሳያልና፥ የእያንዳንዱም ሥራ እንዴት መሆኑን እሳቱ ይፈትነዋል።									
									    
								 
- 
									
									14
									 
									 
									|1 Corintios 3:14|
									ማንም በእርሱ ላይ ያነጸው ሥራ ቢጸናለት ደመወዙን ይቀበላል፤									
									    
								 
- 
									
									15
									 
									 
									|1 Corintios 3:15|
									የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጎዳበታል፥ እርሱ ራሱ ግን ይድናል ነገር ግን በእሳት እንደሚድን ይሆናል።									
									    
								 
- 
									
									16
									 
									 
									|1 Corintios 3:16|
									የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?									
									    
								 
- 
									
									17
									 
									 
									|1 Corintios 3:17|
									ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 14-15