- 
			
				
- 
									
   Amharic (NT)									 - 
									
									 
- 
									
									3
									 
									 
									|1 Corintios 2:3|
									እኔም በድካምና በፍርሃት በብዙ መንቀጥቀጥም በእናንተ ዘንድ ነበርሁ፤									
									    
								 
- 
									
									4
									 
									 
									|1 Corintios 2:4|
									እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም።									
									    
								 
- 
									
									6
									 
									 
									|1 Corintios 2:6|
									በበሰሉት መካከል ግን ጥበብን እንናገራለን፥ ነገር ግን የዚችን ዓለም ጥበብ አይደለም የሚሻሩትንም የዚችን ዓለም ገዦች ጥበብ አይደለም፤									
									    
								 
- 
									
									7
									 
									 
									|1 Corintios 2:7|
									ነገር ግን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከዘመናት በፊት ለክብራችን የወሰነውን፥ ተሰውሮም የነበረውን የእግዚአብሔርን ጥበብ በምሥጢር እንናገራለን።									
									    
								 
- 
									
									8
									 
									 
									|1 Corintios 2:8|
									ከዚችም ዓለም ገዦች አንዱ እንኳ ይህን ጥበብ አላወቀም፤ አውቀውስ ቢሆኑ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር፤									
									    
								 
- 
									
									9
									 
									 
									|1 Corintios 2:9|
									ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።									
									    
								 
- 
									
									10
									 
									 
									|1 Corintios 2:10|
									መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር በመንፈሱ በኩል ገለጠው።									
									    
								 
- 
									
									11
									 
									 
									|1 Corintios 2:11|
									በእርሱ ውስጥ ካለው ከሰው መንፈስ በቀር ለሰው ያለውን የሚያውቅ ሰው ማን ነው? እንዲሁም ደግሞ ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር ለእግዚአብሔር ያለውን ማንም አያውቅም።									
									    
								 
- 
									
									12
									 
									 
									|1 Corintios 2:12|
									እኛ ግን ከእግዚአብሔር እንዲያው የተሰጠንን እናውቅ ዘንድ ከእግዚአብሔር የሆነውን መንፈስ እንጂ የዓለምን መንፈስ አልተቀበልንም።									
									    
								 
- 
									
									13
									 
									 
									|1 Corintios 2:13|
									መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያይተን መንፈስ በሚያስተምረን ቃል ይህን ደግሞ እንናገራለን እንጂ የሰው ጥበብ በሚያስተምረን ቃል አይደለም።									
									    
								 
 - 
									
 - 
				
Sugerencias
 

Haga clic para leer Juan 14-15