-
-
Amharic (NT)
-
-
14
|Lucas 21:14|
ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤
-
15
|Lucas 21:15|
ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና።
-
16
|Lucas 21:16|
ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤
-
17
|Lucas 21:17|
በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
-
18
|Lucas 21:18|
ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤
-
19
|Lucas 21:19|
በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ።
-
20
|Lucas 21:20|
ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ።
-
21
|Lucas 21:21|
የዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በመካከልዋም ያሉ ከእርስዋ ፈቀቅ ይበሉ፥ በገጠር ያሉም ወደ እርስዋ አይግቡ፤
-
22
|Lucas 21:22|
የተጻፈው ሁሉ እንዲፈጸም ይህ የበቀል ጊዜ ነውና።
-
23
|Lucas 21:23|
በዚያን ወራት ለእርጕዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው፤ ታላቅ ችግር በምድር ላይ፥ በዚህም ሕዝብ ላይ ቍጣ ይሆናልና፤
-
-
Sugerencias
Haga clic para leer Números 31-32